March 30, 2018, 11:25 p.m. by EtMDB
ድርጅታችን ቢንያም የንግድ ፕሮሞሽን አገልግሎት ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በቅርቡ በመጪዉ ግንቦት ወር ላይ ታላቅ አገር አቀፋዊ የብረታ ብረት አና ኢንጅነሪንግ ፣ኤሌክትሪካል እና ኤሌክትሮኒክስ፣ ኬሚካልና የኮንስትራክሽን ግብአቶች ምርቶች ኤግዚብሽን ለማካሄድ በዝግጅት ሂደት ላይ እንገኝአለን በዚህ ዝግጅት ላይ ተሳትፎ የሚኖራቸዉ ተቐማት ለእያአንዳዳቸው የሁለት ደቂቃ ሽፋን የሚሰጥ የሥራ አመራሮችን የተመረጠ ጥያቄ ኢንተርቪዉ እና የየተቓማቱን የሥራ ሒደት እና እንቅስቃሴ የሚያሳይ ደረጃዉን የጠበቀ የቪዲዮ ዶክመንተሪ እንዲሰራልን እንፈልጋለን ..እነዚህ ቁጥራቸዉ ከ300 በላይ እንደሚሆን የሚጠበቁ ተቓማት በአዲስ አበባ እና በአዲስ አበባ ዙሪያ 100ኪ.ሜ ንፍቀ ክበብ ዉስጥ የሚገኙ ሲሆን በእናንተ በኩል 10 የካሜራ ባለሙያዎችን የያዘ ቡድን አደራጅታችሁ እንደምትሰጡን እና በአፋጣኝ ወደ ስራ እንደምንገባ በአቶ መላኩ ተኮላ በኩል በተደረገ ግኑኝነት የተነገረን ሲሆን ከእናንተ በኩል የተቀላጠፈ ምላሽ እንድትሰጡን እና በተገኙት በድኖች ስራ የምንጀምርበት ሂደት እንድንጀምር ስንል በትህትና እንጠይቃለን.
To apply or for further information please directly contact binyamtradepromotions@gmail.com